Posts

Showing posts with the label ልዩ ልዩ

ዘወትር በልቤ

ለእናቴ ሁሌም የማትጠፊው ዘወትር ከፊቴ አንች ርህሩሂቷ አዛኝቷ እናቴ ጠርቸም አልጠግብሽ ዘወትር በአንደበቴ ስቀመጥ ስነሳ ስሄድም ስመጣ ስቆምም ስተኛ ስበላም ስጠጣ የአንች ትዝታ ነው ከፊቴ ሚመጣ ዘወትር በሀሣቤ ሌላ እንዳላነሳ ከፊቴም አጠፊ ሁሌ አንችን አረሳ በአካል ባላገኝሽ ወደ አንች ቀርቤ በህሌናየ አለሽ ዘወትር በልቤ downloadd

..“አልተግባብቶም”

አካባቢው በጫጫታና በሁከት ተሞልቷል :: ሁሉም መናገራቸውን እንጅ ምን እንደሚናገሩ፣ምን እንደሚነገር፣ ማን እንደሚናገር አያዳምጡም :: ብቻ አፋቸው ያመጣውን፣ ስሜታቸው የሚያዝዛቸውን ይናገራሉ :: ስሜታችው እየጋለ ወደ ድብድብ ሊያመራ ይመስላል :: ሁሉም የኔ ነው ትክክል ! የኔ ነው ትክክል ! በሚል ስሜት ተውጠው የሌላው ሀሳብ አይጥመውም፥ አያዳምጠውምም :: ከመካከላቸው አንዱ “ ይህ እኮ “ ብር ” ነው ምን ነካችሁ ? ይህ እኮ ጫማ፣ ልብስ፣ቲማቲም፣ሽንኩርት የምንገዛበት ብር እኮ ነው ” ይላል :: አንዱ ደግሞ ፀጉሩን እየፈተለ በአንድ እጁ ሱሪውን ይዞ “ ኧረ ሸ ነው ምን ሆናችኋል ? ይህ እኮ ” ጨላ “ ነው ! ቀፍላችሁ አታውቁም እንዴ ?” ይላል :: ሌላው ደግሞ በሲጋራና በጫት የበለዙ ጥርሶቹን እያሳየ “ ኧረ ፍሬንድ አምፖላችሁ ላላ እንዴ ? ይህ   እኮ ” መላ “ ነው ! የበርጫ ምናምን መሸመቻ ነው እኮ ?” ይላል :: አንዱ ሱፍ ይለበሰ ደግሞ “ ወገኖቸ ምን እያላችሁ ነው ? ይህ እኮ ” ገንዘብ “ ነው ! ባንክ አትጠቀሙም እንዴ ? ብትቆጥቡ እኮ ታውቁት ነበር ! ይህ ” ገንዘብ “ ነው !” ይላል :: ከሀሳቡ ይልቅ ምላሱ የሚቀድም ሌላው ደግሞ ” ኧረ ላሽ ይህ ይጠፋችኋል ? ይህ እኮ ” ፍራንክ “ ነው ! ቆይ ከቤተሰብ ፈልጣችሁ አታውቁም እንዴ ?” ይላል :: ሌላው ባለስልጣን የሚመስል ደግሞ ቦርጩን እየገፋ “ አይ ከእውቀት ነፃ መሆን ! ይህ እኮ ” በጀት “ ነው ! ሀገሪቱን እያንቀሳቀሰ ያለው እኮ ይህ ነው ! የተለያዩ መሰረታዊ ...